ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ሊዮ የእግዚአብሔር መንግሥት በጸጥታ የሚያድገው በፍቅር እንጂ በኃይል አይደለም አሉ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በሐምሌ 13/2018 ዓ.ም የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ካደረጉ በኋላ በእለቱ ከማቴዎስ ወንጌል 13፡24-43 ላይ ተወስዶ በተነበበውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሕዝቡ ስለእንክርዳድ፣ የሰናፍጭ እና የእርሾ ምሳሌ በሚገልጸው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው ባደረጉት የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ የእግዚአብሔር መንግሥት በጸጥታ የሚያድገው በትሕትና፣ በትዕግስት እና በፍቅር መሆኑን ገልጸው ክርስቲያኖች በምስጢራዊ በሆነው ሥራ እንዲታመኑ እና በዓለም ላይ "ትንንሽ የወንጌል ዘሮች" እንዲሆኑ አሳስበዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በእለቱ ከማቴዎስ ወንጌል ተወስዶ የተነበበው ኢየሱስ የተናገራቸው ቃላት ዋና ዋና ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

“መንግሥተ ሰማይ በዕርሻው ቦታ ጥሩ ዘር የዘራን ሰው ትመስላለች። ነገር ግን ሰው ሁሉ ተኝቶ ሳለ፣ ጠላቱ መጥቶ በስንዴው መካከል እንክርዳድ ዘርቶ ሄደ።ስንዴው በቅሎ ማፍራት ሲጀምር እንክርዳዱም ዐብሮ ብቅ አለ።

መንግሥተ ሰማይ አንድ ሰው ወስዶ በዕርሻው ቦታ የዘራትን የሰናፍጭ ዘር ትመስላለች። የሰናፍጭ ዘር ከሌሎች ሁሉ ያነሰች ብትሆንም፣ ስታድግ ግን ከአትክልት ሁሉ በልጣ፣ የሰማይ ወፎች መጥተው በቅርንጫፎቿ ላይ እስኪያርፉ ድረስ ዛፍ ትሆናለች።”

“መንግሥተ ሰማይ ሴት ወስዳ ሊጡ በሙሉ እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት ውስጥ በመደባለቅ የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች።”

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ክርስቲያኖች አስደናቂ የእግዚአብሔርን ኃይል ለማሳየት የምያግዱትን ፈተናዎች እንዲተው አሳስበዋል፣ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ትንሽ ዘር ወይም እንደ ትንሽ እርሾ በማይታይ ሁኔታ እንደሚሠራ በጸጥታ እና በትዕግስት እንደሚያድግ ምእመናንን አስታውሰዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በካስቴል ጋንዶልፎ በሚገኘው የጳጳስ እረፍት ማድረጊያ ቪላ ካለበት ሥፍራ ሆነው እሁድ እለት ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ካደረጉ በኋላ በሥፍራው ለተገኙ ምዕመናን ባደረጉት የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ከቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል የተወሰዱ ሦስት ምሳሌዎችን ማለትም - የስንዴውና የእንክርዳዱ፣ የሰናፍጭ ዘርና እርሾ ምሳሌዎች ላይ ተንተርሰው እግዚአብሔር በታሪክ በወንዶችና በሴቶች ሕይወት ውስጥ የሚሠራበትን መንገድ ገልጸዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሱ ራሱን በኃይል ከማስገደድ ወይም በድል ከመድረስ ይልቅ፣ እግዚአብሔር "ትንሽነትን" መሆንን የልባምነትና የትዕግስት ፍቅሩ ምልክት አድርጎ እንደሚመርጥ ተናግረዋል።

"እሱ እንድንቀበል ወይም እንድንክድ በነፃነት ይተወናል" ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ተናግረዋል። የእግዚአብሔር ፍቅር “በእንክርዳድ መካከል እንኳን መገኘቱን” እንደሚያሳይ፣ እንደ ትንሹ ዘር በማይታይ ሁኔታ እንደሚሰራ እና ዓለምን በዝምታ እንደሚለውጥ በመጥቀስ፣ ሊጥን እንደ ምያቦካ እርሾ ዓለምን ይለውጣል ብለዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሱ ብዙ ሰዎች እግዚአብሔር በከፍተኛ ሁኔታ ጣልቃ እንዲገባ እና ክፉውን ወዲያውኑ ከዓለም እንደሚያስወግድ እንደሚጠብቁ አምነዋል። እንዲህ ያሉት ግምቶችን መውሰድ እንደሌለብን አስጠንቅቀው፣ የክርስቲያን ሕይወትንና የቤተክርስቲያንን ጤናማ ያልሆነ እይታ ሊቀርጹ ይችላሉ ሲሉ አክለው አሳስበዋል።

በምትኩ፣ ክርስቲያኖች መንግሥቱ በክፉ ነገሮች መካከል እንኳን እንደሚያድግ እንዲገነዘቡ ተጠርተዋል ያሉ ሲሆን ይህ በጨለማ ውስጥ እያለፈ የሚመጣን መልካም ነገር መለየት፣ የችኮላ ፍርድ ለመስጠት የምያስገድዱንን ፈተናዎች መቋቋም እና ቀስ በቀስ የእግዚአብሔርን ጸጋ ሥራ በትዕግስት ማጀብ ይጠይቃል ብሏል።

ቅዱስነታቸው አክለውም መንግሥቱ፣ ብዙውን ጊዜ በተለመደው የዕለት ተዕለት ሕይወት ጊዜያት ውስጥ ይታያል፣ ሳይስተዋል እየሄደ ቢሆንም ያለማቋረጥ በሥራ ላይ ነው ያሉ ሲሆን እግዚአብሔር ባይኖርም እንኳ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ እንዳሉት ከሆነ፣ ሁልጊዜም አለ እና ፍቅሩ ሁል ጊዜ ለመርዳት ዝግጁ መሆኑን ለምዕመናን  አረጋግጠዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ፣ የእግዚአብሔር የተግባር መንገድ ክርስቲያኖች በግልም ሆነ በቤተክርስቲያን አባላት የአኗኗር ዘይቤ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

አማኞች “ወንጌልን ማዕከል ያደረገ አቀራረብ” ብለው የገለጹትን እንዲቀበሉ፣ እብሪትን፣ ሌሎችን የመግዛት ፍላጎትን ወይም እምነትን ለመጫን ኃይልን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ አበረታተዋል። በምትኩ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ጸጥተኛ ሥራ ላይ እምነታቸውን ሊጥሉ ይገባል ብለዋል።

የቀድሞውን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት 16ኛ፣ በወቅቱ ካርዲናል ጆሴፍ ራትዚንገር ተብለው ይጠሩ የነበሩትን በመጥቀስ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ክርስቲያኖች “የዘርን (የህል ዘር) አመክንዮ” እንዲቀበሉ ተጠርተዋል፣ ይህም “የስኬትና የታላቅነት ሳይሆን ራሳችንን ትንሽ ማድረግና ሌሎችን ማገልገል” ነው።

በዚህ መንገድ፣ ክርስቲያኖች “ትንንሽ የወንጌል ዘሮች” እና “የፍቅር እርሾ” ሊሆኑ ይችላሉ ያሉት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ምእመናንን ለቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አደራ ሰጥተዋል፣ የእግዚአብሔርን ቃል ዘር በትህትና የተቀበሉት፣ ክርስቲያኖች በእምነት ጉዞአቸው ላይ እንዲደግፉ ከጠየቁ በኋላ ቅዱስነታቸው አስተንትኗቸውን አጠናቀዋል።

20 Jul 2026, 16:10

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >