“ፅንስ ማስወረድ እውነተኛ ምርጫ ሊሆን ፍጹም አይችልም”
የዚህ ዝግጅት አቅራቢ ዮሐንስ መኰንን - ቫቲካን
“በኮሎምቢያ ምዕራባዊ ክፍል ነሐሴ 4/2018 ዓ. ም. በሬክተር መለኪያ 7.4 ያስመዘገበ ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱ ይታወሳል። በአደጋው ከ200 በላይ ሰዎች መሞታቸውን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ መቁሰላቸውን ሪፖርቶች አስታውቀዋል። በወቅቱ የተቀረጹት የቪዲዮ ምስሎች አንዲት እናት በፍርስራሽ ውስጥ አዲስ የተወለደ ልጇን እና ራሷን ከሞት ለማዳን ስትጥር አሳይተዋል።
በማኅበራዊ ሚዲያዎች እና በዜና ማሰራጫዎች በኩል ይፋ የሆኑት እነዚህ ምስሎች የውድመቱን ክብደት፣ የአደጋ ጊዜ ሠራተኖች ጥድፊያ እና እናት ከልጇ ጋር በሕይወት መትረፋቸውን የሚያሳዩ ናቸው። ምስሉ በሁሉም ረገድ ነፍስን ማዳን እና መንከባከብ፣ የሌላውን ኃላፊነት መውሰድ፣ ራስን ለማዳን ያለመ ወንድማማች እና ደጋፊ ማኅበረሰብ እንዳለ የሚያሳይ ነው። ዓላማው “ይህን ለማድረግ ምን ያህል አቅም ያስፈልጋል?” የሚል ሳይሆን ሕይወትን ከሞት ማዳን ብቻ ነው።
በ4,300 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኝ ዩናይትድ ስቴትስ ከተማ ማሳቹሴትስ ውስጥ ትዕይንቱ ፈጽሞ የተለየ ነው። በእናቱ ማህፀን ውስጥ ያለ የአንድ ልጅ ሕይወት በተመሳሳይ መንገድ አይታይም።
በአካባቢው “ለታካሚው ቅድሚያን የሚሰጥ እንክብካቤ” የሚል ሕግ ጸድቋል። ይህ ሕግ በፈቃደኝነት እርግዝናን ለማቋረጥ የሚያስችል የሃያ አራት ሳምንታት ገደብን ያስቀረ እና ሐኪሙ በሙያዊ ፍርድ ውሳኔ እንዲያደርግ የሚያስችል ነው። በዚህ ሕግ ውስጥ “እንክብካቤ” የሚለው ቃል ቢኖርም ሞትን የሚደግፍ ነው። አሜሪካ ውስጥ ፅንስ በማስወረድ ላይ ጠቅላላ ገደቦችን የማያስቀምጡ አሥር ግዛቶች አሉ። ትኩረት የሚሰጡት ለሕይወት አይደለም።
በዓለም ዙሪያ ደረጃ በደረጃ በፖለቲካ ትክክለኛነት ወይም በርዕዮተ ዓለም ግጭት እና ተቃውሞ በሰው ላይ የሚደርስ የሞት አደጋ እየተስፋፉ ይገኛል። በዚህ ዓመት ብቻ ሉክሰምበርግ በሕገ መንግሥቷ ውስጥ ፅንስ ማስወረድ የመጠቀም ነፃነትን አካትታለች። በቻርተሯ ውስጥ በግልጽ ካስቀመጠች ፈረንሳይ ቀጥላ ሁለተኛዋ ሀገር ስትሆን ዩናይትድ ኪንግደም በበኩሏ ከቁጥጥር ማዕቀፏ ውጭ ፅንስ ማስወረድን ትደግፋለች።
በእናት ማህፀን ውስጥ ያለ ሕጻን እንዲገደል የሚፈቅዱ ሕጎች በጸደቁባቸው በዓለም ዙሪያ ባሉ ሁሉም አገራት እገዛን ማድረግ፣ መንከባከብ፣ በድጋፍ የሚፈጸም ግድያውን ለመከላከል የታለሙ አንቀጾች አሉ። ነገር ግን ድንጋጌዎቹ እጅግ ከባድ ከመሆናቸው የተነሳ በሁሉም ወይም በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች በተግባር አልተተገበሩም።
ሰዎች የሴቶች ምርጫ ምን ሊሆን እንደሚገባ፣ እንክብካቤ ምን መስምሰል እንዳለበት ይነጋገራሉ።
ቀላል እና ተግባራዊ ሊሆን የሚችል መንገድ ቢኖርም ትክክለኛ የመምረጥ ዕድልን አይሰጡም። ወዲያውኑ ጣልቃ በመግባት ችግሩን ማስወገድ እና ሰው እያንዳንዱን ሳይንሳዊ ግኝቶች እንዳይክድ የሚያደርግ ሂደት እንዲጀምር ያሳስባል።
በምትኩ አንዲት ሴት እውነተኛ ምርጫን እንድታደርግ መፍቀድ ማለት መንገዶችን ሥነ ልቦናዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መንፈሳዊ ድጋፍ ማድረግ ማለት ነው። ነገር ግን ይህ በገንዘብ እና በሃብት ረገድ ወሰን የለሽ ከፍተኛ ወጪ ያለው በመሆኑ ዝም ማለት ይሻላል።
አንድ ሀገር ዜጎቹን ሲጠብቅ፣ ሰላምን፣ እኩልነትን፣ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ሲያረጋግጥ፣ ለሁሉም አርቆ አሳቢነት እና የእይታ ስፋት እንዳለው ያሳያል። ዜጎች ሌላውን ማወቅ፣ መርዳት፣ መደገፍ መንከባከብ እና መውደድ የሚጀምሩት ለወደፊቱ መሠረት የሚጥል ማኅበረሰብ ሲገነቡ ነው። በዚህ ጊዜ ፅንስ ማስወረድ ትክክል ወይም ስህተት፣ ሕይወትን የሚጻረር እና የመደገፍ ማረጋገጫ መንገድ ይሆናል።
መዛባት የሚመጣው መከራን፣ ችግርን እና ስቃይን ለመደበቅ ሲሞከር ነው፣ ይልቁንም ራሳቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያገኟቸውን እና መውጫውን ማግኘት የማይችሉትን ማካተት ከመፈለግ ነው።
የሰው ልጅ ማንነት የሚለካው በመግደል ሳይሆን እርስ በእርስ በመዋደድ እና ኃላፊነትን ሲወስድ ነው። ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሙሉ በሙሉ በደስታ በመሞላት በፍርስራሽ ውስጥ ተቀብሮ የሚገኘውን ሕይወት ለማዳን ፈቃደኛ ይሆናል።”