ፈልግ

የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ 

ከእዚህ ቀደም ያልታተሙ የር.ሊ.ጳ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከቶች በእንግሊዝኛ ቋንቋ ታትመው ይፋ ሁኑ!

የቫቲካን ማተሚያ ቤት (LEV) ቀደም ሲል ታትመው ለንባብ ያልበቁ የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከቶች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ባገለገሉበት ወቅት እና ከርዕሰ ሊቃነ ጵጵስናቸው በገዛ ፈቃዳቸው ከለቀቁ በኋላ ባሳረጓቸው የግል መስዋዕተ ቅዳሴዎች ወቅት የቀረቡትን ቀደም ሲል ያልታተሙ ስብከቶች አንድ ላይ የሚያሰባስብ የእንግሊዝኛ እትም ለንባብ አቅርቧል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

"ጌታ በእጃችን ይዞናል" የሚለው አዲስ የእንግሊዝኛ ቋንቋ እትም ለአንባቢዎች ቀደም ሲል ያልታተሙትን የሊቀ ጳጳስ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከቶች ስብስብ ያቀርባል፣ ይህም እርሳቸው እንደ ሰባኪ፣ የሃይማኖት ምሁር እና የቤተክርስቲያን እረኛ ድምጽ እንደገና እንዲሰሙ ያስችላቸዋል።

ይህ ጥራዝ መጀመሪያ በቫቲካን ማተሚያ ቤት " Il Signore ci tiene per mano"  (ጌታ እጃችንን ይይዘናል) በሚል ርዕስ በጣሊያንኛ ቋንቋ የታተመ ሲሆን እ.አ.አ ከ2005 እስከ 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በስብከተ ገና ሰሞን ወቅት፣ በዐቢይ ጾም እና በፋሲካ የአምልኮ ወቅቶች የተሰጡ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ስብከቶችን አሰባስቦ ይዟል።

በአቶ ሪካርዶ ቦላቲ፣ ሉካ ካሩሶ እና በአባ ፌዴሪኮ ሎምባርዲ፣ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ የሊቀ ጳጳስ ቤኔዲክቶስ 16ኛ የግል ጸሐፊ የነበሩት ሊቀ ጳጳስ ጆርጅ ጋንስዌይን የመቅድም ጽሑፍ እና የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ የቫቲካን ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት የሆኑት አባ ሎምባርዲ የመግቢያ ጹሑፍን ያካትታል።

የግል መስዋዕተ ቅዳሴዎች፣ የህዝብ ምስክር

ስብከተ ወንጌሎቹ የተደረጉት በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ከሊቀ ጳጳስ ቤተሰብ እና አልፎ አልፎ ከእንግዶች ጋር በማክበር በ “የግል” መስዋዕተ ቅዳሴዎች ላይ ያደረጓቸው ስብከቶች ሲሆኑ እርሳቸው ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ጊዜ እና በኋላም ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳስናቸው በገዛ ፈቃዳቸው ከተነሱ በኋላ በግል ባስረጓቸው መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያደረጓቸውን ስብከቶች ያጠቃለለ እንደሆነም ተገልጿል።

ምንም እንኳን በግል ቦታዎች የተነገሩ ቢሆኑም፣ ጽሑፎቹ የቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከት ጥልቀት እና በተመሳሳይ ጊዜም ቀለል ብለው መቀረቡ መሆናቸው ያሳያል።  ቅዱስ ቁርባንን በአዲስ መንገድ የማንበብ ችሎታቸውን ያሳያሉ፣ ለእምነት፣ ለጸሎት እና ለዕለታዊ የክርስትና ሕይወት ብርሃንን ይሳሉ።

ክርስቶስ መሃል ላይ

የመጽሐፉ ገጾች የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔድክቶስ 16ኛ በእምነታቸው መሃል ላይ እንዴት እንደቆዩ ያሳያሉ፤ ረቂቅ ወይም ደረቅ አስተሳሰብ ሳይሆን ከክርስቶስ ጋር የግል ግንኙነት በመፍጠር እንዴት መኖር እንድሚገባን በሚገባ እንደምያሳዩ በስብከቶቹ ውስጥ የገለጹ ሲሆን፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ሕዝቡን የሚከተል፣ የሚደግፋቸው እና በእጃቸው የሚይዛቸው ጌታ ምስጢር ደጋግመው መግለጻቸው ይታወሳል።

ርዕሱ ራሱ ይህንን ማዕከላዊ ግንዛቤ ይገልፃል፡ የክርስቲያን ሕይወት ብቸኛ መንገድ ሳይሆን በእግዚአብሔር መገኘት እና ምሕረት የሚመራ ጉዞ ነው የሚል ጭብጥ የስብከታቸው መአከል ሲሆን የስብከታቸው ስብስብ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ሥነ-መለኮታዊ ሥራ እና በእረኝነት አገልግሎቱ መካከል ያለውን ቀጣይነት ያጎላል። የእርሳቸው አስተንትኖዎች ግልጽነት፣ መንፈሳዊ ጥልቀት እና የጵጵስና ሥልጣናቸውን በሚለይ በክርስቶስ ላይ ያተኮሩ በመሆናቸው  ተለይተው ይታወቃሉ።

ሰፋ ያለ ፕሮጀክት

"ጌታ እጆቻችንን ይይዘናል" በሚል አርእስት የታተመው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከቶች የመጀመሪያ ጥራዝ ነው። ከመደበኛው ጊዜ ለተሰጡ ስብከቶች የተሰጠ ሁለተኛ ጥራዝ እንደሆነም ተገልጿል።

የጣሊያን እትም እ.አ.አ በግንቦት 17/2026 ዓ.ም ቀን በቱሪን ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ትርኢት ላይ “ቤኔዲክቶስ 16ኛ፡ ‘ክርስቶስ የወደፊት ነው!’ በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ስብሰባ ላይ ቀርቦ እንደ ነበረ ይታወሳል።

ከተሳታፊዎቹ መካከል አባ ሎምባርዲ እና ጣሊያናዊው ዘፋኝ እና ጸሐፊ ጆቫኒ ሊንዶ ፌሬቲ ይገኙበታል፣ ውይይቱን የመሩት ደግሞ በቫቲካን ዜና ዋና አርታይ   የሆኑት አቶ አንድሪያ ቶርኒሊ ነበሩ።

የእንግሊዝኛው እትም ሲታተም፣ እነዚህ ቀደም ሲል ያልታተሙ ጽሑፎች አሁን ሰፋ ያለ አንባቢዎች ይገኛሉ፣ ይህም የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ስብከት እና ክርስቶስን በእምነት እና በታሪክ እምብርት ላይ እንዲያስቀምጡ ያቀረቡትን የዕድሜ ልክ ግብዣ በማቅረብ ነው።

 

25 Jun 2026, 15:28