የቅድስት ማርያም ሜጀር (ዐብይ) ባዚሊካ ቅዱስ በር ማክሰኞ ምሽት ጥር 05/2018 ዓ.ም ማታ አንድ ሰዓት ላይ  በተዘጋበት ወቅት የቅድስት ማርያም ሜጀር (ዐብይ) ባዚሊካ ቅዱስ በር ማክሰኞ ምሽት ጥር 05/2018 ዓ.ም ማታ አንድ ሰዓት ላይ በተዘጋበት ወቅት   (@VATICAN MEDIA)

የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ባዚሊካዎች ቅዱስ በሮች እስከሚቀጥለው ኢዮቤልዩ ድረስ ዝግ ሆነው ይቆያሉ!

የቅድስት መንበር የፕሬስ ጽኃፈት ቤት የአራቱ ጳጳሳት ባዚሊካዎች ቅዱስ በሮች የሚታሸጉበትን ይፋዊ ያልሆነ ሥርዓቶች የጊዜ ሰሌዳ ይዘረዝራል። በቅድስት መንበር የፕሬስ ጽ/ቤት መግለጫ መሠረት፣ በዚህ ሳምንት በሊቀ ጳጳሳት ባዚሊካዎች ውስጥ የቅዱሳን በሮች መታሸግ ይፋዊ ያልሆነ ሥነ ሥርዓቶች እየተጠናቀቀ ነው።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

የቅድስት ማርያም ሜጀር (ዐብይ) ባዚሊካ ቅዱስ በር ማክሰኞ ምሽት ጥር 05/2018 ዓ.ም ማታ አንድ ሰዓት ላይ እስከሚቀጥለው የኢዩቤሊዩ አመት ድረስ ዝግ ሆኖ እንዲቆይ ታሽጓል።

ሥነ ሥርዓቱ ረቡዕ ዕለት በጥር 06/2018 ዓ.ም በቅዱስ ዩሐንስ ላተራን ባዚሊካ ቅዱስ በር በመዝጋት የቀጠለ ሲሆን ሐሙስ በጥር 07/2018 ዓ.ም የቅዱስ ጳውሎስ ባዚሊካ ቅዱስ በር እስከሚቀጥለው የኢዩቤሊዩ አመት ድረስ ታሽጎ ዝግ ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የመጨረሻው ሥነ ሥርዓት አርብ ምሽት ጥር 08/2018 ዓ.ም የቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ቅዱስ በር የሚታሸግ ሲሆን እስከሚቀጥለው የኢዩቤሊዩ አመት ድረስ ዝግ ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

እንደ መግለጫው ከሆነ፣ እንደተለመደው በሥነ ሥርዓቱ ወቅት በማሸጊያው ውስጥ የነሐስ ሳጥን ይቀመጣል።

የቅዱስ በር መዘጋት፣ የበሩ ቁልፍ፣ እ.አ.አ ከ2016 ዓ.ም የመጨረሻ መዝጊያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የተመዘገቡ በርካታ የጳጳሳት ሜዳሊያዎችን እና በሚገኙበት ቦታ ሁሉ የባዚሊካ የመታሰቢያ ሜዳሊያን ኦፊሴላዊ መዝገብ ይዟል።

15 Jan 2026, 11:44