ቅድስት መንበር ለሄይቲ ያላትን ድጋፍ በድጋሚ አረጋግጣለች!
የዚህ ዜና አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስቫቲካን
በአሜሪካ መንግስታት ድርጅት ቋሚ ምክር ቤት (OAS) ሁለት የተለያዩ ስብሰባዎች ላይ የቅድስት መንበር ቋሚ ታዛቢ የሆኑት የእኔታ አባ ሁዋን አንቶኒዮ ክሩዝ ሴራኖ፣ ቫቲካን ለሄይቲ ሕዝብ እና በሄሪኬን ሜሊሳ ለተጎዱት ሰዎች ያላትን አጋርነት ገልጸዋል፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሰላም፣ ለመረጋጋት እና ለአካባቢ ጥበቃ በአዲስ ቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀስ አሳስበዋል።
በሄይቲ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ጥሪ
በሄይቲ በክልላዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ድጋፍ የሚመራው የዋና ፀሐፊው “የመረጋጋትና የሰላም መንገድ” የሂደት ሪፖርት ላይ ባቀረቡት ንግግር ላይ የእኔታ አባ ክሩዝ ሴራኖ እንዳሉት ቅድስት መንበር የሄይቲ ሕዝብ የሚያጋጥመውን ከባድ የሰብአዊና ማህበራዊ ተግዳሮቶች በቅርብ ትኩረት እየተከታተለች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
ፍኖተ ካርታውን “በሀይቲ ውስጥ ያለውን አሳሳቢና ድራማዊ የሆነ እውነታ” በሚል ርዕስ ገልጸውታል፤ ይህም በአደጋ፣ በድህነትና በዓመፅ የተሞላ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ እየተባባሰ መምጣቱ ያስከተለውን አውሎ ነፋስ ሜሊሳ ባስከተለው ውድመት ላይ አጽኖት ሰጥተው ተናግረዋል።
በቅርቡ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በዓለም የምግብ ቀን ላይ ለተባበሩት መንግሥታት የእርሻ ድርጅት (FAO) ባደረጉት ንግግር ላይ የእኔታ አባ ክሩዝ እንደ ገለጹት ከሆነ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን ዓለም አቀፍ የአንድነት እና የአጋርነት ጥሪ ደግመውታል፡- “አሁንም እየተሰቃዩ ያሉ ብዙዎች የተራቡ ፊቶች እኛን ይፈታተኑናል፣ እናም የአኗኗር ዘይቤያችንን፣ ቅድሚያ የምንሰጣቸውን ነገሮች እና አጠቃላይ የአኗኗር ዘይቤያችንን እንደገና እንድንመረምር ይጋብዙናል … ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ወደ ሌላ አቅጣጫ ሊመለከት አይችልም። ስቃያቸውን የራሳችን ማድረግ አለብን” ሲሉ የተናገሩትን በድጋሚ አስተጋብተዋል።
የቅድስት መንበር በ55ኛው የተባበሩት መንግሥታት የእርሻ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ሥልጣን መሠረት በእንግሊዜኛው ምጻረ ቃል "OAS" (የአሜሪካ መንግስታት ድርጅት (OAS): በአሜሪካ አገሮች መካከል የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ትብብርን የሚያካትት ባለብዙ ወገን መድረክ ነው) ዋና ጸኃፊ ከተባበሩት መንግሥታት የእርሻ ድርጅት ዓላማዎች ጋር በሚግባባ መልኩ ቀጣይነት ያለው ጥረት ከፍ አድርጎ እንደሚመለከተው እና “ለሄይቲ ሕዝብ ያለውን ቅርበት እና ሰላምንና መረጋጋትን ለማስፈን የታለሙ ተነሳሽነቶችን ሁሉ ያለማቋረጥ እንደሚደግፍ” ተናግሯል።
በአውሎ ነፋሱ ሜሊሳ ከተጎዱት አገሮች ጋር ያለው አንድነት
በሁለተኛ ደረጃ በካሪቢያን አካባቢ ስላለው አውሎ ነፋሱ ተጽእኖ በተወያዩበት ወቅት፣ የቅድስት መንበር ተወካይ “የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ሀዘን፣ ጸሎት እና መንፈሳዊ ቅርበት” ከጃማይካ፣ ሄይቲ፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ ኩባ እና ባሃማስ መንግስታት እና ህዝቦች ጋር ያለውን መንፈሳዊ ቅርበት ገልጸዋል።
አውሎ ነፋሱ ከባድ የጎርፍ መጥለቅለቅ፣ የህይወት መጥፋት፣ መፈናቀል እና በቤቶች፣ በመሠረተ ልማት፣ በትምህርት ቤቶች እና በሆስፒታሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል። የእኔታ አባ ክሩዝ ሴራኖ አክለው እንዳሉት ከሆነ ቤተክርስቲያኗ እንደ ካሪታስ እና የካቶሊክ እርዳታ አገልግሎቶች ባሉ የአካባቢ ማህበረሰቦች እና ድርጅቶች አማካኝነት “በእነዚህ አስቸጋሪ እና እርግጠኛ ባልሆኑ ጊዜያት ለተጎዱት ለመድረስ እየሞከረች ነው” ብለዋል።
ቫቲካን ለሁሉም አገራት እና ሕዝቦች ለሥነ-ምህዳር ኃላፊነት እንክብካቤ ኃላፊነት እንዲወስዱ ያቀረበችውን ጥሪ በድጋሚ አረጋግጠዋል፣ “በተጨባጭ እርምጃዎች እና ከሁሉም በላይ ደግሞ በዋና ዋና ብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ውሳኔዎች ተፈጥሮን መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን” አስታውሰዋል።
ለፍጥረት እንክብካቤ የጋራ ኃላፊነት
ቅድስት መንበር፣ “እንደ የአሜሪካ መንግሥታት ድርጅት በእንግሊዜኛው ምጻረ ቃል "OAS" (በአሜሪካ አገሮች መካከል የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ትብብርን የሚያካትት ባለብዙ ወገን መድረክ ነው) OAS ያሉ ዓለም አቀፍ እና ክልላዊ ድርጅቶች በተፈጥሮ ላይ ስለሚፈጸሙ በደሎች በመንግሥታት እና በሲቪል ማኅበረሰብ መካከል ግንዛቤን በማሳደግ እና የእያንዳንዱን አገር አካባቢ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ለመጠበቅ ኃላፊነት የሚሰጠውን ግዴታ ለመወጣት የታለሙ ዘዴዎችን በማስተዋወቅ ረገድ የሚያደርጉትን ተግባር የሚያስመሰግን ተግባር እንደሆነ አድርጎ ይቆጥረዋል ሲሉ ተናግረዋል፣ “ፍጥረትን መንከባከብ እና መጠበቅ የሁሉም ኃላፊነት ነው” ካሉ በኋላ የእኔታ አባ ክሩዝ ሴራኖ ንግግራቸውን አጠናቀዋል።