ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ   (@VATICAN MEDIA)

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ፣ ጸሎት የተስፋ ተግባር ነው ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ሰነዶች ላይ በተከታታይ የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እያደረጉ እንደምገኝ የሚታወቅ ሲሆን በዚህም መሰረት ቅዱስነታቸው በሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ከእነዚህ የሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ሰንዶች መካከል "ስለ መለኮታዊ ሥርዓተ አምልኮ" በሚገልጸው ዶግማዊ ሕገ ደንብ ዐብይ አርእስት ላይ ተንተርሰው "የቤተ ክርስቲያን ጸሎት" በተሰኘው ንዑስ አርስት ላይ ያተኮረ የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ማድረጋቸው የተገለጸ ሲሆን 'ጸሎት የተስፋ ተግባር ነው" ማለታቸው ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በእለቱ የተነበበው የእግዚአብሔር ቃል

"በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ እስከ መጨረሻው በጽናት ትጉ። ቃል እንዲሰጠኝና አፌን በመክፈት የወንጌልን ምሥጢር በግልጥ እንዳስታውቅ፥ ስለ እኔም ለምኑ" (ኤፌሶን 6፡18-19)።

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በወቅቱ ያደረጉትን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

ወንድሞችና እህቶች፣ እንደምን አረፈዳችሁ!

በዚህ የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ፣ ስለ መልኮታዊ ሥርዓት አምልኮ፣ በላቲን ቋንቋ (Sacrosanctum Concilium (SC)፣ በተሰኘው የሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ዶግማዊ ሰነድ ላይ እያደረግን የምንገኘውን አስተንትኖ ዛሬም እንቀጥላለን። ዛሬ የሥርዓተ አምልኮ ጸሎትን የቤተ ክርስቲያን ገጽታ እንመለከታለን።

ሐዋርያው ​​ጳውሎስ እንደጠቆመው፣ እንድንጸልይ የሚያስተምረን መንፈስ ቅዱስ ነው። ከጴንጤቆስጤ ቀን ጀምሮ፣ መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ውስጥ ይኖራል፣ እያንዳንዱን እንቅስቃሴዋን እና በተለይም ጸሎትን ያነሳሳል። ከኢየሱስ ፋሲካ በኋላ በኢየሩሳሌም የተወለደው የመጀመሪያው ማህበረሰብ ሕይወት፣ ከሙታን በተነሳው ጌታ የተሰጠ በመንፈስ የተነሣው ሕይወት ነው። “ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያን የፋሲካን ምስጢር ለማክበር አንድ ላይ ከመሰብሰብ ተቆጥባ አታውቅም፤ ‘ስለ እርሱ በቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የተጻፉትን’ (ሉቃስ 24:27) ማንበብ፣ ‘በሞቱ ድል መንሣትና ድል እንደገና የተገኘበትን’ መሥዋዕተ ቅዳሴ በዓል ማክበር፣ እና በተመሳሳይ ጊዜ ‘ስለማይነገር ስጦታው ለእግዚአብሔር ምስጋና በማቅረብ’ (2ኛ ቆሮ 9:15) በክርስቶስ ኢየሱስ ‘ለክብሩ ምስጋና’ (ኤፌ. 1:12)፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል’ ምስጋና ማቅረብ” (SC, 6) ተገቢ ነው።

በእኛ ዘመን፣ በብቃት ላይ በተመሠረተ እና በፍጆታ አስተሳሰብ በተሞላ አውድ፣ ጸሎት ትርጉም የለሽ እና ቀላል ሊመስል ይችላል። ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሁሉንም መልሶች እንደሚሰጡ በሚናገሩበት ዓለም፣ ጸሎት የማምለጫ መስክ ሊመስል ይችላል። ከዚህም በላይ፣ በብዙ ክርስቲያን ቤተሰቦች ውስጥ እንኳን፣ የጸሎት ወግ ከእንግዲህ በበቂ መንገድ አይተላለፍም፣ ብዙ ሰዎች ከሌላ ቴክኒክ፣ ከሥነ ልቦናዊ ተፈጥሮ እና ለግል ደህንነት ባለ ዓላማ ብቻ ግራ ሊጋቡ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ጸሎት፣ እንደ ሰብዓዊነታችን መሠረታዊ ገጽታ፣ በእውነተኛ መልኩ እንደገና ማግኘት ተገቢ ነው።

የሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ መለኮታዊ ሥርዓተ አምልኮን የተመለከተ ሰነድ ቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ ይህንን ፍላጎት በቁም ነገር ይመለከቱት ነበር። ይህ ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ ታላቅ ደስታ ምክንያት ነበር፣ በሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ የጸደቀውን የመጀመሪያውን ሰነድ ሲያወጡ እንዲህ ብለዋል፡- “እግዚአብሔር ሁሌም ቀድሞ ይመጣል፤ ጸሎት ዋና ግዴታችን ነው፤ ከአምልኮ ሥርዓቱ ለእኛ የተላለፈልን የመለኮታዊ ሕይወት ዋና ምንጭ፣ የመንፈሳዊ ሕይወታችን የመጀመሪያ ትምህርት ቤት ነው” (እ.አ.አ በታህሳስ 4/1963 ዓ..ም በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ውስጥ ከተናገሩት የተወሰደ) ።

በዶግማዊ ሰነዱ ውስጥ፣ “ጸሎት” የሚለው ቃል ሥርዓተ አምልኮውን በአጠቃላይ ይወክላል። ይህ አመለካከት ወሳኝ ነው፣ ምክንያቱም የአምልኮ ሥርዓቱን ማሻሻያ በመምራት የምእመናንን ንቁ ተሳትፎ ማዕከላዊ ምሰሶ አድርጎታል። ሥርዓተ አምልኮ በመጀመሪያ ደረጃ የሚቀርበው እግዚአብሔር በልጁ “ሥጋ የሆነውን ቃል፣ በመንፈስ ቅዱስ የተቀባ” (SC, 5) ውስጥ ለሰው ልጅ በመቅረብ የጀመረበት ተነሳሽነት ሲሆን፣ “በክርስቶስ አማካይነት፣ ከእርሱ ጋር፣ በእርሱ ሥም እና በመንፈስ ቅዱስ አንድነት” ምላሽ ልንሰጥ እንችላለን፣ ማለትም “ክርስቶስ ራሱ ከሥጋው ጋር ለአብ የሚያቀርበው ጸሎት” (SC, 84) ምስጋና ይገባዋልና ነው።

በዚህም ምክንያት፣ ቅዱስ ጳውሎስ 6ኛ የሰዓታት ጸሎት፣ የቤተ ክርስቲያን ዕለታዊ የሕዝብ ጸሎት፣ ከቅዱስ ቁርባን የማይለይ፣ ሁሉንም የክርስቲያናዊ ጸሎት በጥልቀት እንዲገባ፣ ሕያው እንዲያደርግ፣ እንዲመራ፣  እንዲገልጽ እና የእግዚአብሔርን ሕዝብ መንፈሳዊ ሕይወት ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲመግብ ከልባቸው የፈለጉበት ምክንያት ነበር።

ይህ ፍላጎት እውን እንዲሆን፣ የሰዓታት ጸሎት በተጠመቁትና በማህበረሰቦች የዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ሙሉ በሙሉ መካተትና መኖር አለበት። መጸለይን ለመማር ለሚፈልጉ ብዙ ሰዎች፣ በተለይም ንዑሰ ክርስቲያኖች (የሐይማኖት ትምህርት ተማሪዎች) የክርስቲያን ጸሎት መንገድና ትምህርት ሊያቀርብ ይችላል።

በየሳምንቱና በየቀኑ፣ ቅዱስ ቁርባንና የሰዓታት ጸሎት የቤተክርስቲያን የሕይወት እስትንፋስ ናቸው፣ ይህም መንፈስ ቅዱስ በሰውነቷ ውስጥ እንዲዘዋወር ያደርጋል። በዚህ ጸሎት፣ ክርስቶስ “ከዚህ የመለኮታዊ ምስጋና መዝሙር ጋር ከማያያዝ ጋር የሰውን ዘር ሁሉ ማኅበረሰብ ወደ ራሱ ይቀላቀላል” (SC, 83)። በዚህ መንገድ፣ በየቀኑ፣ ከፋሲካ ምስጢር ጋር እየተባበርን እና ከእርሱ ጋር እየታረቅን እንሄዳለን።

ቅዱስ አውጎስጢኖስ “እግዚአብሔርን በጸሎት ምሕረትን ስንጠይቅ፣ ልጁን ከእርሱ አንለየውም፤ የወልድም ሥጋ ሲጸልይ፣ ​​ራሱን ከራሱ አይለይም፤ እርሱም የአካሉ አንድ አዳኝ ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እርሱም ስለ እኛ የሚጸልይ፣ በእኛም የሚጸልይ፣ ከእኛ ጋር አብሮ የሚጸልይ ነው። እንደ ካህናችን ይጸልያል፤ በእኛም እንደ አምላካችን ይጸልያል። ስለዚህ ቃላችንንና በእኛም ውስጥ ያለውን ቃል በእርሱ እንወቅ” ሲሉ ጽፈው ነበር።

ብርሃንን የሚያራዝመውን ቅዱስ ቁርባንን በመያዝ፣ የሰዓታት ጸሎት የዕለት ተዕለት የሕይወታችንን ጊዜ ይቀድሳል፤ የጥዋት ጸሎት ቀኑን በእምነትና በምስጋና እንድንጀምር ይረዳናል፣ የእኩለ ቀን ጸሎት፣ በድካማችን መካከል ታማኝ ሆነን ለመቀጠል ጥንካሬን እንድንጠይቅ ያደርገናል፣ የምሽት ጸሎት፣ ሥራችን ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የጸሐይ መጥለቂያ ጊዜን ይከተላል፤ የሌሊት ጸሎት፣ ለእግዚአብሔር ሰላም ራሳችንን አደራ በመስጠት በሰላም እንድንተኛ ያረዳናል። የእያንዳንዱ የጸሎት ሰዓት የተስፋ ተግባር ነው፡- በምድራዊ ጉዞአችን ወቅት፣ ከመላው ቤተክርስቲያን ጋር በመሆን የጌታን ክብር ለመመለስ በጸሎት እንጠባበቃለን።

05 Aug 2026, 15:28