ዩክሬይን እና ራሻ የምያደርጉት ጦርነት ያስከተለው መዘዝ ዩክሬይን እና ራሻ የምያደርጉት ጦርነት ያስከተለው መዘዝ  (AFP or licensors)

ር.ሊ.ጳ ሊዮ በጦርነት ምክንያት የሚሰቃዩትንና የሚሞቱትን ሰዎች መዘንጋት የለብንም አሉ!

በካስቴል ጋንዶልፎ፣ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት እና በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ አስተንትኖ ካደረጉ በኋላ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ “በጦርነትና በዓመፅ በተበታተኑ የተለያዩ አገሮች ውስጥ የሚከሰቱት ክስተቶች ሁሌም እንደምያሳስባቸ እና ጉዳዩ በሰላም ይፈታ ዘንድ ጸሎት ማድረግ እንደሚቀጥሉ" ተናግረዋል። ሁሉም ሰው “የማያቋርጠውን ጸሎታችንን፣ ለሰላም በትጋት አጥብቀው ለመጸለይ እንዲተባበሩ" አሳስበዋል። በተጨማሪም ፒያሳ ዴላ ሊበርታ በተሰኘው ሥፍራ የተሰበሰቡትን በርካታ ምዕመናንን ተቀብለው ሰላምታ አቅረበውላቸው እንደ ነበረም ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

በካስቴል ጋንዶልፎ በሚገኘው የሐዋርያዊ የማርፊያ ቤት መግቢያ ላይ፣ ከሕዝቡ ጋር ለመገናኘት እና የእሑድ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎትን ብቻ በማድረግ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጭንቀታቸውንና ሀሳባቸውን እንደገና ዓለምን አሁንም በሚነኩ በርካታ ግጭቶች ላይ አተኩረዋል።

“በጦርነትና በዓመፅ በተበታተኑ የተለያዩ አገሮች ውስጥ የሚከሰቱትን ክስተቶች መከተላችንን እንቀጥላለን። በእነዚህ ግጭቶች ምክንያት እየተሰቃዩና እየሞቱ ያሉትን አንርሳ፣ እና ለሰላም ለጋስ ጥረቶች የማያቋርጥ ጸሎታችንን ማድረግ እንቀጥል” ሲሉ ቅዱስነታቸው ተናግረዋል።

በዩክሬን የተጎዱ ሰዎች እና በኢራን እና ኩዌት የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች የተከሰቱ ሪፖርቶች

ዛሬ በዩክሬን ግጭት የሟቾች ቁጥር ሪፖርት ተደርጓል፣ ዋና ከተማዋ ኪየቭ በከባድ የሩሲያ ሚሳኤል ጥቃት ተመትታ አንድ ሰው ተገሎ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎችን ቆስለዋል ተብሎ ተዘግቧል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩክሬን ጦር በጥቁር ባህር እና በአዞቭ ባህር ውስጥ በሩሲያ ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ዘመቻዎችን እንዳካሄደ ተናግሯል። በተመሳሳይ ጊዜ በደቡብ ኢራን አዳዲስ የአሜሪካ የአየር ድብደባዎች ሪፖርት ተደርገዋል፣ ከዚያም ቴህራን በኩዌት ውስጥ የአሜሪካ ወታደራዊ ጭነቶችን ኢላማ በማድረግ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ተኩሳ ነበር። በኢራቅ ኩርዲስታን ተገለዋል ተብሏል።  ዋሽንግተን አዲሱን ጥቃት ባለፈው አርብ በዮርዳኖስ በሚገኘው ሙዋፋክ አል ሳልቲ የአየር ጣቢያ ላይ ከተፈጸመው ጥቃት ጋር አያይዛዋለች፣ በዚህ ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ተገድለዋል እና ሶስተኛው ደግሞ እስካሁን የት እንዳለ እንደ ማይታወቅ ተነግሯል።

ለካስቴል ጋንዶልፎ ነዋሪዎች እና ለጉብኝት ምዕመናን ሰላምታ አቅርቧል

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ከዚያም የካስቴል ጋንዶልፎ ነዋሪዎችን ሁሉ ሰላምታ እና ምስጋናቸውን አቅርበው "ከሁሉም የዓለም ክፍሎች የመጡ ምዕመናንን" በደስታ ተቀብለዋል። ለሕይወት በዓል በሳሉዞ በተሰበሰቡት እና በማሆይ ኤልቪራ ለተቋቋመው የፎኮላሬ ማህበር ንቅናቄ አባላት ልዩ ሰላምታ አቅርበዋል።

በእንግሊዝኛ ንግግር ያደረጉት ቅዱስነታቸው፣ የሬኙም ክሪስቲን ወጣት አዋቂ አባላትን እንዲሁም በሲድኒ ረዳት ጳጳስ አንቶኒ ፐርሲ የታጀቡ "የላዮን መንፈሳዊ ነጋዲያን"  የተሰኘውን ዓለም አቀፍ የስልጠና ኮርስ ተሳታፊዎች ሰላምታ አቅርበዋል።

 

20 Jul 2026, 16:07