ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በእስፔን የምያደርጉት ሐውርያዊ ጉብኝት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በእስፔን የምያደርጉት ሐውርያዊ ጉብኝት   (@Vatican Media)

ለተገለሉ ሰዎች የሚደረግ መንፈሳዊ እንክብካቤ

የቫቲካን ዜና የአርታኢ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አንድሪያ ቶርኒዬሊ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሊዮ ለስፔን ምዕመናን የተናገሯቸው ቃላት ለመላው ቤተክርስቲያን መንገድ እንዴት እንደሚያመለክቱ ያብራራሉ።

አንድሪያ ቶርኒዬሊ

ውስጣዊ ለውጥ እንድናመጣ የምያደርጉን የግል አምልኮዎች ወይም የቤተክርስቲያኗን ያለፈውን ማህበራዊ ተጽዕኖ በናፍቆት የሚያስታውሱ ሙዚየም አይደሉም፣ ነገር ግን እውነተኛ ትምህርት ቤት ነው። ለቁርጠኝነት፣ ለመገናኘት፣ ለመቀበል እና ራስን ለመስጠት የሚከፍት ትምህርት ቤት። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በማድሪድ ውስጥ በፕላዛ ደ ሲቤሌስ በተከበረው የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም በዓል መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ባደረጉት ስብከት ስፔንን የፈጠረውን ሃይማኖታዊነት የገለጹት በዚህ መንገድ ነው። በሁደት፣ በሕዝብ አምልኮ፣ በሥነ ጥበብ፣ በሙዚቃ እና በሥነ ሕንፃ አማካኝነት የሚገለጽ ሃይማኖታዊነት።

"በመንገዶች ላይ የሚሄደው ክርስቶስ" ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ "ከድሆች፣ ከተገፉ፣ ብቻቸውን እና ከተተውት ጋር የሚገናኝ ህያው ክርስቶስ ነው።" በስፔን ውስጥ ቤተክርስቲያኗ ከረጅም ጊዜ በፊት የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም ክብረ በዓልን ከበጎ አድራጎት ቀን ጋር አቀላቅላ ማክበሯ የአጋጣሚ ነገር አይደለም። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ለስፔን ግልጽ ግብዣ አቅረበዋል፣ ታዋቂ ሃይማኖታዊ እምነት በሕይወት ባለበት አገር፣ “በቀድሞ ጊዜ እንደ ነበረ ሙዚየም የሚጎበኝ ሳይሆን ዛሬም ቢሆን የምንጎበኘው የእምነት ትምህርት ቤት መሆን የለበትም፡- ማንም ሰው በጌታ ፊት ተንበርክኮ ወንድሙን ሊንቅ ስለማይችል በእግዚአብሔር ፊት እና በባልንጀራችን ፊት እንድንበረከክ የሚያስተምረን ትምህርት ቤት፤ ስጦታ የሚሆነውን ፍቅርን ያለክፍያ የሚያስተምረን፣ በመካከላችን እንዲፈስ እና የራስ ወዳድነት ሰንሰለት እንዲሰብር የሚያስተምረን ትምህርት ቤት፤ እግዚአብሔር እውነተኛ መገኘት መሆኑን እና እኛም በኅብረተሰቡ እውነታዎች እና ተግዳሮቶች ውስጥ እንድንገኝ የተጠራንበት ትምህርት ቤት፣ ሳንሸሸግ፣ ነገር ግን በግል ለጋራ ጥቅም ግንባታ ራሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ የተጠራንበት ትምህርት ቤት” ሊሆን ይገባል።

እነዚህ ቃላት በቀጥታ የሚናገሩት በጠንካራ ዋልታ ረገጥ ማኅበረሰብ ውስጥ፣ ክፍፍልና ሞቅ ያለ ውዝግብ በተደጋጋሚ በሚከሰትበት ጠንካራ ጥራዝ ነጠቅ ማኅበረሰብ ውስጥ የስፔን ክርስትናን የሕይወት ተሞክሮ ነው። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በመጀመሪያ ክርስቲያኖች የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም መልእክትን ልብ እንዲረዱና እንዲኖሩ ጥሪ አቅርበዋል፤ ይህም የሚቀርበውና በተራው እንድንቀርብ የሚጠይቀን፣ በሚሰቃይ፣ ምግብ ወይም መጠለያ በሌለው ወይም ስደተኛ በሆነ ወንድም ወይም እህት ውስጥ እሱን የሚያውቅ አምላክ ነው። ከዚህ አንፃር፣ የቤተክርስቲያኗ ማህበራዊ ጠቀሜታ የሚገኘው በአገልግሎት ውስጥ ነው፡- ለድሆች ፍላጎቶች ምላሽ በመስጠት፣ እርቅን በማበረታታት፣ ዋልታ ረገጥነትን በማሸነፍ፣ ለፍትህ በመስራት እና የበለጠ ሁሉን አቀፍ ማህበረሰብ በመገንባት።

"የቅዱስ ቁርባን ኢየሱስ" ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ "የተደበቀ ዘላለማዊ ምንጭ፡ የሚፈስና ጥማትን የሚያረካ ምንጭ ነው፣ ነገር ግን ሳያሳውር፣ በውጫዊ ኃይል ራሱን ሳያስገድድ፣ በሚያስደንቅ ሁኔታ ራሱን ሳያቀርብ" በሥውር የሚገለጽ ነው። በዚህ ምክንያት፣ የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም ሕዝባዊ በዓል “በግል አምልኮ ውስጥ ብቻ አያካትተንም፣ ነገር ግን ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን፣ ቤተሰቦቻችንን፣ ድሆችን፣ ስቃዮችን እና ተስፋቸውን ያጡ ሰዎችን ለማደስ ይልከናል። የቅዱስ ቁርባን ጸጋ ይለውጠናል እና የታሪክ ለውጥ ዋና ገፀ-ባህሪያት ያደርገናል፣ ለምናገኛቸው ሰዎች የተስፋ ምልክት” ይሆነናል።

ክርስቲያኖች ዓለምን በመናፍስትና በጠላቶች እየሞሉ ሁሉንም ነገር ግልጽ የሚያደርጉ በሚመስሉ ተቃራኒ ግጭቶች፣ ንፁህ ቀላል አቀራረቦች እና ማንነትን መሰረት ባደረጉ አቀራረቦች ውስጥ ከመጠመድ አደጋ ነፃ አይደሉም። በዚህ ምክንያት፣ የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም በዓል ሁደት ታሪካዊ ትዝታ “በአስቂኝ ናፍቆት ብቻ የተወሰነ” ሳይሆን “በአሁኑ ጊዜ፣ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን፣ በግንኙነታችን፣ በኅብረተሰቡ ውስጥ” የቀረበ ግብዣ መሆኑ አስፈላጊ ነው። በሌላ አነጋገር፣ ለሰው ልጅ ልብ ለእርቅና ለሰላም ጥማት ምላሽ ለመስጠት አገልግሎት ይሆናል።

 

08 Jun 2026, 11:05