እ.አ.አ ህዳር 25 ቀን 2022 ዓ.ም. በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃትን ለማስወገድ የተከበረው ዓለም አቀፍ ቀን እ.አ.አ ህዳር 25 ቀን 2022 ዓ.ም. በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃትን ለማስወገድ የተከበረው ዓለም አቀፍ ቀን 

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት፡ በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት አቅልለን እንዳንመለከተው አሉ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ወርሃዊውን የፒያዛ ሳን ፒዬትሮ መጽሔት ላይ ባሰፈሩት ጹሑፍ የሴት ልጅ ግርዛትን የሚያወግዝ እና በትምህርት ቤቶች እና በቤተክርስቲያን መካከል “የመከባበር ባህል” እንዲሰፍን ጥሪ አቅርበዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በዚህ ወር ፒያዛ ሳን ፒዬትሮ መጽሔት እትም ላይ ለአንባቢው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፣ ይህም እ.አ.አ መጋቢት 8 ቀን በዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን መከበሩ ይሚታወቅ ሲሆን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ፣ እንደተለመደው፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እርዳታ ወይም አስተያየት እና መመሪያ ለጠየቁት አንባቢ ምላሽ ሰጥተዋል። በመጋቢት ወር እትም ላይ፣ ደብዳቤው የተፈረመው በሮም በምትገኘው ጂዮቫና ነው። “በእንባ በተሞላ አይኗ” ሆና መልክቱን እንደ ጻፈች የምትናግረው ጆቫና “ወንድን መውደድ፣ ማግባት ወይም ከእሱ ጋር መኖር እና ቤተሰብ መፍጠር” የሚለው ለብዙ ሴቶች አሳዛኝ ሁኔታ ቃል አቀባይ በመሆን “እንባ እያነባች” ጽፋለች።

“ለምን?” ብላ ትጠይቃለች። “ዛሬ ብዙ ወንዶች እንደሚወዷቸው በሚገልጿቸው ሴቶች ላይ የሚፈጽሟቸውን ዓመፅ እና ጥቃት፣ አሁን በጣም በተደጋጋሚ እና በሚያምሙ፣ እንዴት ማስረዳት እንችላለን? እስከ መግደል ደረጃ ድረስ። በጭካኔ፣ በጥላቻ፣ ልክ እንደነሱ መውደድ እንዳቆሙ ጥፋተኛ እንደሆኑ ይታያሉ ስትል ጥያቄ” አቅርባለች።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ምላሽ ረጅም እና አሳቢ ሲሆን የሚጀምረው ይህ ጉዳይ የፈጠረውን “ታላቅ ስቃይ” ስሜት በመግለጽ ነው፡- “በግንኙነቶች ውስጥ የሚፈጸም ጥቃት፣ በተለይም በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃት” በማውሳት ምላሻቸውን የጀመሩ ሲሆን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊን እና “በአመፅ አስተሳሰብ በተሞላ ዓለም” ፊት መደገፍ ያለበትን ታዋቂውን አገላለጽ ጠቅሰዋል።

ሴቶች “ለሁሉም የሰው ልጆች የወደፊት እና ክብር ለመስጠት አስፈላጊ የሆነውን የእንክብካቤ እና የወንድማማችነት ባህል ፈጣሪዎች ናቸው” ይላሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ። “ምናልባት በዚህ ምክንያት” ዛሬ የዓመፅ ኢላማዎች ሊሆኑ ይችላሉ፣ “ተገርፈው እና ተገድለዋል” ምክንያቱም “በዚህ ግራ በተጋባ፣ እርግጠኛ ባልሆነ እና በዓመፀኛ ማህበረሰብ ውስጥ የክርክር ምልክት ናቸው፣ ምክንያቱም ወደ እምነት፣ ነፃነት፣ እኩልነት፣ ትውልድነት፣ ተስፋ፣ አንድነት እና ፍትህ እሴቶች ስለሚጠቁሙን ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

እነዚህ በምትኩ “ግንኙነቶችን የሚበክል አደገኛ አስተሳሰብ የሚቃወሙ ሲሆን ራስ ወዳድነትን፣ ጭፍን ጥላቻን፣ መድልዎንና የበላይነትን ብቻ የሚያመነጩ ሐሳቦች ሊወገዙ ይገባል” ብለዋል።

እ.አ.አ ባለፈው ሰኔ 8/2025 ቀን በዋለው የጴንጤቆስጤ በዓል ላይ፣ እንዲሁም የንቅናቄዎች ኢዮቤልዩ በዓል ላይ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ ቀድሞ ባደረጉት ስብከት፣ ብዙውን ጊዜ ወደ ዓመፅ የሚያመራውን ይህንን አመለካከት አውግዘው ነበር፣ ይህም በሚያሳዝን ሁኔታ በቅርብ ጊዜ በተከሰቱት በርካታ እና የቅርብ ጊዜ የሴት ግድያ ጉዳዮች ታይቷል። “ዓመፅ፣ ማንኛውም ጥቃት፣ ሥልጣኔን ከአረመኔነት የሚለየው ድንበር ነው” ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

አንድ ሰው የዓመፅ ድርጊትን በፍፁም ዝቅ አድርጎ ማየት የለበትም እና ሪፖርት ለማድረግ መፍራት የለበትም ብለዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሊዮ በተጨማሪም ጂዮቫና ስለ ባህል እና ስለ ወጣቶች ትምህርት “ከመሠረቱ” ለስራ ባቀረበችው ጥሪ እንደተገረሙ ተናግረዋል፣ ይህም ለሴቶች እና ለሌሎች በአጠቃላይ ከእኛ የተለዩ ሰዎች አክብሮት እንዲኖራቸው ይረዳል። በአባታችን ኤንዞ ፎርቱናቶ የሚመራው የመጽሔቱ አንባቢዎች እንደገለጹት፣ ይህ የትምህርት ቤቱ ሥርዓትና ቤተክርስቲያን አብረው ሊያከናውኑት የሚችሉት ሥራ ነው፡-

“ትምህርት ቤትና ቤተክርስቲያን ካልሆነ በስተቀር፣ አዲሶቹን ትውልዶች የመከባበር፣ የፍቅር እና ከሁሉም በላይ የነፃነት ባህል በማስፋፋት ማን ሊረዳቸው ይችላል? ሰዎች ሴትን እንደ አንድ ነገር አድርገው እንዳይቆጥሩ የሚያስተምር መልእክት… ያስፈልጋል” ብለዋል።

ስለዚህ ለጂዮቫና “ከዚህም በላይ ጠንካራ የትምህርት ጥምረት” ጥሪ አቅርበዋል፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ፍጹም አስፈላጊነትን እንዲህ ሲሉ ደግመው ይገልጻል፣ “ለጋራ ሰብአዊነታችን በጋራ መከባበር አብሮ መጓዝ ህልም አይደለም፣ ነገር ግን ለሁሉም ሰው የብርሃን ዓለም ለመገንባት ብቸኛው ሊሆን የሚችል እውነታ ነው” ሲሉ በደብዳቤው ላይ ጽፈዋል።

ቤተክርስቲያኗ፣ ከቤተሰቦች፣ ከትምህርት ቤቶች፣ ከደብሮች፣ ከንቅናቄዎችና ከማህበራት፣ ከምዕመናን እና ከሕዝብ ተቋማት ጋር በመሆን፣ በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለመከላከልና ለማስቆም የተወሰኑ ፕሮጀክቶችን የማዘጋጀት አጣዳፊነት መጋራት ትችላለች ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ እ.አ.አ ባለፈው ህዳር 25 ቀን በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለማስወገድ በተከበረው ዓለም አቀፍ ቀን ላይ ከተገለጸው “ዓመፅን ማስቆም” እና “ወጣቶችን በአዲስ መልክ መፈጠር” በመጀመር “እያንዳንዱ ሰው ክብር የሚገባው ሰው ነው፣ ለወንዶችም ለሴቶችም ክብር ይገባዋል” ለማለት የሁሉም ሰው ልብ ለመክፈት መሞከርን የሚያመለክት ተጨማሪ ጥሪ አቅርበው ነበር።

“ይህንን ዓመፅ ማስወገድ አለብን” ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ደምድመዋል፣ “እና አስተሳሰባችንን ለመቅረጽ መንገዶችን መፈለግ አለብን። ለሁሉም የሚያስቡ የሰላም ሰዎች መሆን አለብን” ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

09 Mar 2026, 10:55