ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ በዩክሬን እና በጦርነት በተጎዱ ክልሎች ሁሉ ሰላም እንዲሰፍን ጥሪ አቅርበዋል
የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ እሁድ ዕለት በግጭት በተጎዱ ክልሎች ሰላም እንዲሰፍን ጥሪ አቅርበዋል፣ ዩክሬን፣ መካከለኛው ምስራቅ እና ሌሎች ሰዎች በጦርነት ምክንያት የሚሰቃዩባቸውን አካባቢዎች አጉልተው በመልእክታቸው የገለጹት ቅዱስነታቸው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ከተነበበ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ትኩረታቸውን በዩክሬን ውስጥ እየደረሰ ወደ ሚገኘው ቀጣይነት ያለው ስቃይ አዙረዋል፣ “በእነዚህ ቀናትም ቢሆን ዩክሬን ያለማቋረጥ በሚሰነዘር ጥቃት እየተመታች በመምጣቷ መላው ህዝብ ለክረምት ቅዝቃዜ እንዲጋለጥ ሆነዋል” ብለዋል።
“እየተከናወነ ያለውን ነገር በሀዘን እከታተላለሁ፣ ከሚሰቃዩት ጋር ቅርብ ነኝ፣ እና ለእነሱም እጸልያለሁ” ያሉት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ እናም የተራዘመው ግጭት “ለሲቪሎች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከባድ መዘዝ እንደሚያስከትል፣ በሕዝቦች መካከል ያለውን ልዩነት እንደሚያሰፋ እና ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ አስቸጋሪ” እንደምያደርግ ቅዱስነታቸው ተናግረዋል።
“ጦርነቱን ለማስቆም ሁሉም ሰው ጥረቱን እንዲያጠናክር እጠይቃለሁ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ቃላት የመጡት ዩክሬናውያን እና የሩሲያ አስታራቂዎች በአቡ ዳቢ በአሜሪካ የተደገፉ የፊት ለፊት ውይይቶችን ለማድረግ በተዘጋጁበት ወቅት ነው። ሁለቱ ወገኖች በሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ ላይ በዩክሬን ከተሞች እና በመሠረተ ልማት ላይ ከፍተኛ የሞት መአት ብያስከትልም በአሜሪካ የሚመራ ቀጥተኛ የሰላም ውይይት ለማድረግ መስማማታቸውን ተዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በሮም አደባባይ ላይ የተገኙትን የካቶሊክ አክሽን ወጣቶችን ሰላም ሲሉ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ “ለሰላም ጉዞ” ሕይወት ለመስጠት ላደረጉት ተነሳሽነት እና “እኛ አዋቂዎች ዓለምን ከሌላ አቅጣጫ እንድናይ ስለረዳችሁን፣ ይህም በሰዎች እና በተለያዩ ህዝቦች መካከል ስላለው ትብብር” ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
“በቤት፣ በትምህርት ቤት፣ በስፖርት፣ በየትኛውም ቦታ” የሰላም ገንቢዎች እንዲሆኑ በማሳሰብ “በቃላትም ሆነ በተግባር” እና ክፋት በመልካም ነገር እንደሚሸነፍ በፍጹም ዓመፀኛ እንዳይሆኑ ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው ጋብዘዋል።
“ከእነዚህ ወጣቶች ጋር በመሆን፣ በዩክሬን፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በሚያሳዝን ሁኔታ ሰዎች የሕዝባቸው ጥቅም ላይ ባልዋሉባቸው ክልሎች ሁሉ ለሰላም እንጸልይ። ሰላም የሚገነባው ለሰዎች አክብሮት ነው!” ብለዋል።
