ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 'የሰው ልጅ የሚናግረው ቃል ሥጋ ከለበሰ ጀምሮ ነው ማለታቸው ተገልጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ የገና በዓል ጠዋት መስዋዕተ ቅዳሴን እ.አ.አ በታኅሳስ 25/2025 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ያሳረጉ ሲሆን የእግዚአብሔር ቃል ሥጋ ሆኖ “በሰውነት ውስጥ አሁን ይናገራል፣ እኛን ለማግኘት የእግዚአብሔር ፍላጎት ይጮኻል” በማለት በስብከታቸው ገልጸዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

በቅዳሴው ላይ፣ ቅዱስ አባታችን “አዲስ ቀን መጥቷል” እና “እኛም የዚህ አዲስ ጅምር አካል ነን፣ ምንም እንኳን ጥቂቶች ቢያምኑም፣ ሰላም እውን ሊሆን የሚችል ነገር ነው፣ እናም በመካከላችሁ አለ” ሲሉ የተናገሩ ሲሆን ኢየሱስ፣ ደቀ መዛሙርቱን የሰላም መልእክተኞች አድርጎ ልኳቸዋል፣ እነሱም “የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን ኃይል” የሆነውን ቃል ማለትም በሕፃኑ ኢየሱስ “የሚታይ፣ መናገር የማይችል” የሚለውን ቃል ይገልጣሉ ሲሉ ተናግረዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ “ሥጋ” የሚለው ቃል በቤተልሔምም ሆነ በቀራንዮ ላይ ቃል የሌለው ሥር ነቀል የሆነ ቃል ነው ሲሉ አብራርተዋል።

ሆኖም፣ የእግዚአብሔር ቃል ሥጋ ስለሆነ፣ “የሰው ልጅ አሁን ይናገራል፣ እኛን ለማግኘት የእግዚአብሔርን ፍላጎት ይዞ ይጮኻል” ያሉ ሲሆን “ቃሉ ደካማ ድንኳኑን በመካከላችን አስቀምጧል። ታዲያ በጋዛ ውስጥ ለሳምንታት ዝናብ፣ ነፋስና ቅዝቃዜ የተጋለጡትን ድንኳኖች እንዴት ማሰብ አንችልም? እንዲሁም በሁሉም አህጉር ላይ ያሉ ሌሎች በርካታ ስደተኞችና ተፈናቃዮችን? ወይስ በከተሞቻችን ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤት የሌላቸው ሰዎች ጊዜያዊ መጠለያዎችን?” ሲሉ ቅዱስ አባታችን አስታውሰዋል።

በጦርነት በሚሰቃዩ ሁሉ እና የጦር መሣሪያ ለመታጠቅ በተገደዱ ወጣቶች ላይ የሰው ሥጋ “ድክመት” እንደነበር አስታውሰዋል፣ “በግንባር ላይ ያሉት ሰዎች የሚጠየቁትን ነገር ትርጉም የለሽነት እና ወደ ሞት የሚልኳቸውን ሰዎች የኩራት ንግግሮች የሚሞሉትን ውሸት የሚሰሟቸው” ናቸው ያሉ ሲሆን የሌሎች ደካማነት “ልባችን ሲገባ፣ ህመማቸው ግትር የሆኑ ሰዎች እርግጠኛነታችንን ሲሰብር”፣ ያ ሰላም “አስቀድሞ ተጀምሯል” ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ ነው የገና በዓል ለሚስዮናዊቷ ቤተክርስቲያን አዲስ ማበረታቻ የሚሰጠው፣ በእግዚአብሔር ቃል ለእሷ በተዘጋጁት መንገዶች ላይ እንድትገኝ የሚያበረታታት መንገድ ነው ሲሉ አክለው ተናግረዋል።

“ይህ የተልእኮ መንገድ ነው” ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የተናገሩ ሲሆን “ወደ ሌሎች የሚወስድ መንገድ። በእግዚአብሔር ውስጥ፣ እያንዳንዱ ቃል የተነገረ ቃል ነው፤ ለውይይት ግብዣ፣ በራሱ ውስጥ የማይዘጋ ቃል ነው። ይህ ሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ያበረታታው እድሳት ነው፣ ይህም ፍሬ የሚያፈራው ከመላው የሰው ልጅ ጋር አብረን ስንሄድ ብቻ ነው” ሲሉ አብክረው ተናግረዋል።

“የምስጢረ ሥጋዌ እንቅስቃሴ የውይይት ተለዋዋጭ መንገድ ነው” ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ የተናገሩ ሲሆን በመጨረሻም “አንደበታችን ሲቋረጥ እና በማዳመጥ ስንበለጽግ፣ በሌላው ሰው ሰብአዊነት ፊት ስንንበረከክ ሰላም ይኖራል” ካሉ በኋላ ቅዱስነታቸው ስብከታቸውን አጠናቀዋል።

የገና በዓል መስዋዕተ ቅዳሴ በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ሲከናወን
25 Dec 2025, 15:48