የእስራኤል እና የሐማስ ውጊያስ ያስከተለው ውድመት እና ሰቆቃ የእስራኤል እና የሐማስ ውጊያስ ያስከተለው ውድመት እና ሰቆቃ   (AFP or licensors)

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ለተቸገሩ ሕፃናት ፀረ-ባክቴሪያ መድኅኒቶችን ወደ ጋዛ መላካቸው ተገለጸ!

በመጨረሻም ወደ ጋዛ ሰርጥ የሰብአዊ እርዳታ እንዲደርስ ሲደረግ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ የጳጳሳዊ በጎ አድራጎት ድርጅት ጽ/ቤት በሁለት ዓመት ግጭት ውስጥ እጅግ በጣም ተጎጂ ለሁኑ ሕጻናት መድኃኒት እንዲላክ መመሪያ ሰጥተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዩክሬን የምግብ እርዳታ ማከፋፈሉ ቀጥሏል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ባለፈው እሁድ ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አሥራ አራተኛ በኩል በተካሄደው የብስራተ ማርያም ጸሎት  በመቀጠል የተቀሰቀሰው “የተስፋ ብልጭታ” በቅድስት ሀገር የበለጠ ተጨባጭ ቅርፅ ያለው በሚመስልበት ዘመን የጳጳሱ ቅርበት ለሕጻናት እና ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን የመንከባከብ ተጨባጭ ምልክት ይሆናል።

በጳጳስ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጽ/ቤት በኩል፣ “የጳጳስ ሊዮ የመጀመሪያ እርዳታ አገልግሎት” በመባል የሚታወቀው፣ 5,000 ፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶች ወደ ጋዛ ተልከዋል፣ እነዚህም በሁለት ዓመታት ግጭት በጣም ለተጎዱ ሕጻናት እና እናቶች የሚከፋፈሉ መድኅኒቶች እንደሆኑም ተገልጿል።  ይህ እውን ሊሆን የቻለው አሁን የሰብአዊ ርዳታ ለጋዛ ሰርጥ ህዝብ እየደረሰበት ያለው መስቀለኛ መንገድ እንደገና በመከፈቱ ነው።

የርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በጎ አድራጎት አገልግሎት ጽ/ቤት ዋና አስተባባሪ ብፁዕ ካርዲናል ኮንራድ ክራጄቭስኪ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ “ስለድሆች የጻፉትን (በላቲን ቋንቋ የ "ዲሌክሲ ቴ" (ወደድኳችሁ) የተሰኘው ሐዋሪያዊ ቃለ ምዕዳን በተግባር እያዋልን ነው” ሲሉ የገለጹት ዋና አስተባባሪው አክለውም “ለተቸገሩት ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው” ብለዋል።

የጳጳሱ ጽሑፍ የቤተ ክርስቲያኒቱን ተልእኮ በግልጽ ያመለክታል፣ “የወንጌል መሰበክ የሚታመነው በተጨባጭ የመቀራረብና የእንኳን ደህና መጣችሁ መግለጫ ሲሰጥ ብቻ ነው” የሚለውን ሐቅ አጉልቶ ያሳያል ብለዋል።

ለእየሩሳሌም የላቲን ፓትርያርክ ምስጋና ይግባውና የተላኩት ፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶች (አንቲባዮቲኮች) ለተቸገሩት ተሰራጭተዋል። ብፁዕ ካርዲናል አክለው እንደገለጹት በጦርነት ዓመታት ውስጥ እንኳን ለምግብ እና ነዳጅ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በመላክ ለመርዳት ጥረት ሲደረግ እንደነበር አስታውሰዋል።

15 Oct 2025, 15:10