ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
Inizio - Solomon Oratorio in 3 atti HWV 67, per soli, coro e orchestra
መርዐ-ግብር በድምጽ የቀረበ ዘገባ
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ እየታከሙበት የሚገኘው የጂሜሊ ሆስፒታል ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ እየታከሙበት የሚገኘው የጂሜሊ ሆስፒታል   (AFP or licensors)

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በሆስፒታል ውስጥ ጥሩ ምሽት ማሳለፋቸው ተገለጸ!

አርብ ማለዳ የካቲ 28/2017 ዓ.ም የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳትን የጤና ሁኔታ አስመልክቶ የቅድስት መንበር የዜና ማሰራጫ ቢሮ እንደዘገበው ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ሐሙስ ምሽት ሌሊቱን በተረጋጋ ሁኔታ ማሳለፋቸው ገልጿል።

የቅድስት መንበር የዜና ማሰራጫ ጽ/ቤት አርብ ማለዳ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ “ጳጳሱ ምሽቱን በመልካም እረፍት አሳልፈዋል" ሲል አስረድቷል።  

ሐሙስ ዕለት፣ የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራችስኮስ የጤና ሁኔታ ምንም ዓይነት "የመተንፈስ ችግር" ሳይታይበት የተረጋጋ ሆኖ አልፏል ሲል የቅድስት መንበር የዜና ማሰራጫ ጽ/ቤት የገለጸ ሲሆን "የጤና ሁኔታቸው ​​የተረጋጋ ከሆነ ቀጣዩ የህክምና ገለጻ ቅዳሜ ይወጣል" ሲል አክሎ ገልጿል። ነገር ግን የፕሬስ ጽ/ቤቱ ስለ ቅዱስ አባታችን አጫጭር መረጃዎችን መስጠቱን ይቀጥላል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ የካቲት 7/2017 ዓ.ም ሆስፒታል ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ በሁለትዮሽ የሳንባ ምች በሽታ በመጠቃታቸው የተነሳ በሮማ ከተማ በሚገኘው የጂሜሊ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑ ይታወቃል።

የእርሳቸው የሁለትዮሽ የሳንባ ምች በሕክምና ውስጥ የዚህ ዓይነቱ ሁኔታ መደበኛውን ዝግመተ ለውጥ ይከተላል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ከታዘዙት የሕክምና ዘዴዎች ጋር በንቃት ይተባበራሉ፣ ስሜታቸውም መልካም ነው።

የጳጳሱ ዶክተሮች ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ቀውሶች አለመኖራቸውን ያብራራሉ፣ ነገር ግን ለተጨማሪ ግምገማዎች ጊዜ ያስፈልጋል። የጤና ሁኔታቸው  ሁኔታ ውስብስብ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ቢገኝም የተረጋጋ ሆኖ ይቆያል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ 21 ቀናት ያህል በሆስፒታል ውስጥ አሳልፈዋል።

 

07 Mar 2025, 13:24
Prev
March 2025
SuMoTuWeThFrSa
      1
2345678
9101112131415
16171819202122
23242526272829
3031     
Next
April 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930